tg-me.com/addistechshow/1639
Last Update:
🧲🧲🧲በ2014 የ5ጂ ሞባይል ቴክኖሎጂ ሙከራ እንደሚደረግ ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ!
በበጀት ዓመቱ የ5ጂ ሞባይል ቴክኖሎጂ ሙከራ እንደሚደረግ ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል።የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፍሬሕይወት ታምሩ የኢትዮ ቴሌኮም የ3 ዓመት ስትራቴጂና የ2014 በጀት ዓመት እቅድን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
በበጀት ዓመቱ 3.8 ሚሊዮን ተጨማሪ ደንበኞችን ለማስተናገድ የሚያስችል የሞባይል ኔትዎርክ አቅም ለመገንባት እቅድ እንደተያዘም ተገልጿል። የአገልግሎት ጥራትን፣ ተደራሽነትን አና የደንበኞች ተሞክሮን ለማሻሻል የሚያስችል የኔትዎርክ እና ሲስተም አቅም ማሳደጊያ ፕሮጀክቶች እንደሚካሄዱም ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ገልጸዋል።ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ 70 ቢሊየን ብር ለማግኘት አቅዶ እየሠራ እንደሆነ አስታውቋል።
🧲😔በአዲስ አመት
ኢትዮ- ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ ለደንበኞች ምቹና ቀልጣፋ የሆኑ አዳዲስ አሰራሮችን ይተገብራል ብለዋል።
በአሰራሩ ቅናሽ የተደረገባቸውን ጨምሮ ከዚህ በፊት ያልነበሩና ደንበኞች በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገለገሉባቸውን አሰራሮች ይተግብራል ብለዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ከዛሬ ጀምሮ ፓኬጅ ሲጠቀሙ የ20 በመቶ ቅናሽ ያገኛሉ።
በአዲስ አመት ለአንድ ወር የሚቆይ አደይ አበባ የተሰኘ የሞባይል ፓኬጅ አገልገሎት 44 በመቶ ቅናሽ ተደርጎበት ስራ ላይ ይውላል ብለዋል።
የንግድ ተቋማት ፓኬጅ ገዝተው በአጭር የፅሁፍ መልእክት መረጃ የሚቀያየሩበት የ68 በመቶ ቅናሽ ያለው አሰራርም ይጀመራል ብለዋል።
Via EBC
#AddisTechShow
@AddisTechShow
BY Addis Tech Show

Share with your friend now:
tg-me.com/addistechshow/1639